የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት ማስ/ጽ/ቤት ከአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት እና ከጋሞ ዞን ጋር በመተባበር የግድቡ ግንባታ የተጀመረበት 13ኛ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ «የአባይ ዘመን ትውልድ ታላቅ የሥነ ጽሑፍ  ምሽት» “በኅብረት ችለናል!” በሚል መሪ ቃል ግንቦት 09/2016 ዓ/ም በዩኒቨርሲቲው ያካሂዳል፡፡ በዕለቱ መርሃ ግብር ላይ በህዳሴው ግድብ ዙሪያ ላይ ያተኮሩ ግጥሞችንና አጭር ትውን ተውኔቶችን ማቅረብ የምትችሉ ተማሪዎች የሥነ ጽሑፍ ሥራዎቻችሁን ዩኒቨርሲቲው አወዳድሮ ከ1ኛ - 3ኛ የወጡ የተማሪዎች የሥነ ጽሑፍ ሥራዎች በመድረኩ እንዲቀርቡ ዕድል ለመስጠት ስለተፈለገ ከሚያዝያ 15-30/2016 ዓ/ም ድረስ ሥራዎቻችሁን በዩኒቨርሲቲው ኢ-ሜይል አድራሻ፡- This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. ወይም This email address is being protected from spambots. You need JavaScript enabled to view it. በመላክ ወይም የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ጽ/ቤት የመወዳደሪያ ጽሑፋችሁን በሶፍት ኮፒ በመያዝ  በአካል በማቅረብ መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እየገለጸ ተማሪዎቻችን ዕድሉን በማግኘትና በዚህ ሀገራዊ መድረክ ላይ በመገኘት በሥነ ጽሑፍ ጥበብ የበኩላችሁን መልዕክት እንዲታስተላልፉ ከወዲሁ ያሳውቃል፡፡

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን፣ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት ባህልና ቱሪዝም ቢሮና ከጋርዱላ ዞን ጋር በመተበበር የዲራሼ ብሔረሰብ ባህላዊ የትንፋሽ ሙዚቃ መሣሪያ(ፊላ) በዩኔስኮ የሰው ልጆች ወካይ የማይዳሰስ ቅርስ ሆኖ እንዲመዘገብ በተዘጋጀ ረቂቅ ትልመ ሃሳብ(Draft Project Proposal) ዙሪያ በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሚያዝያ 12/2016 ዓ/ም ውይይት ተካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

Arba Minch University (AMU) Research Team wins $100,000 Funding of the Armauer Hansen Research Institute, AHRI, call for Grand Challenges Ethiopia (GCE). The Project is entitled “AI-Based Malaria Incidence Prediction under Current and Future Climate in Southern Ethiopia, AIM-Clim”. The AIM-Clim project brings together experts from diverse research fields including climate science, public health, artificial intelligence, and ecology.

አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር በደቡብና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች በተመረጡ ስድስት ከተሞች ውስጥ በሚኖሩ አፍላ ወጣቶችና ወጣቶች ላይ የአደንዛዥ ዕፅ ተጠቃሚነት የስርጭት መጠን፣ መንስዔዎች እና የሚያስከትለውን ጉዳት አስመልክቶ የሠራውን ጥናት ሚያዝያ 10/2016 ዓ/ም በሶዶ ከተማ ለባለድርሻ አካት ይፋ አድርጓል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡

የአርባ ምንጭ የኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት ከጀርመን ልማት ኤጀንሲ/GIZ/ ጋር በመተባበር የነፃ ሕግ ድጋፍ አገልግሎት ለሕገ ወጥ የሰዎች ዝውውር ተጠቂዎች ለማድረስ ያለመ የጋራ ትብብር ፕሮጀክት የማስጀመሪያና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና መርሃ ግብሮችን ሚያዝያ 7/2016 ዓ/ም አካሂዷል፡፡ተጨማሪ ፎቶዎችን ለማየት እዚህ ይጫኑ፡፡